መጽሐፍ ቅዱስ ሰዎች ብዙ ጊዜ “በግል መዳናችንን ማስረገጥ እንችላለን ወይስ አንችልም?” ብለው ለሚጠይቁት ጥያቄ መልስ ይሰጠን ይሆን? አንድ ሰው ኃጢያቱ ይቅር እንደተባለለት ያውቅ ይሆን? ወይስ ለማወቅ የፍርድ ቀን እስኪመጣ መጠበቅ ይኖርበታል? ይህን ወሳኝ ጥያቄ ለመመለስ እስከዚያን ቀን መቆየቱ አለመታደልና በጣም አደገኛ ውሳኔ ነው፡፡ አዎን፤ የፈለገ ሰው ማወቅ ይችላል፡፡ ጌታም ስለመዳናችን እርግጠኛ እንድንሆን ይፈልጋል፡፡ “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ” (ማቴ. 11፥28) እያለ ጥሪውን እያቀረበልን ነው፡፡ በዮሐ.3፥16 “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን (ኃጢያተኛውን፤ ሁሉንም) እንዲሁ ወዶአልና” ሲል ይነግረናል፡፡ ሰው ሁሉ ከፍጥረቱ ኃጢያተኛ በመሆኑ የእግዚአብሔርን ፍቃድ ከማድረግ ጎድሏል፡፡
በመጀመሪያ አለማችን ባዶ ነበረች፡፡ አሶች በባህር፣ ከዋክብት በሰማይ ላይ አልነበሩም፤ ባህርና ውብ አበቦች የሉም ነበር፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ነበር፡፡ እግዚአብሔር አስደናቂ እቅድ ነበረው፡፡ ውብ የሆነች አለምን ለመስራት አሰበ፡፡ እንዳሰበም ፈጠራት፡፡ እግዚአብሔር አለምን ሲፈጥር ከምንም ነው የሰራት፡፡ “…..ይሁን” አለ፤ ሆነም! ብርሀንን ፈጠረ፡፡ ወንዞችንና ባህርን፣ በሳር የተሸፈነች ምድርን፣ እንስሳትን፣ አእዋፋትንና ዛፎችን ሁሉ ሰራ፡፡ በመጨረሻ ሰውን ፈጠረ፡፡ ለፈጠረው ሰውም ሚስትን አበጀለት፡፡ ስማቸውም አዳምና ሔዋን ይባል ነበር፡፡ እግዚአብሐር አዳምና ሔዋንን በጣም ይወዳቸው ነበር፡፡ ይኖሩበት በነበረበት በውቡ ገነት ሁልግዜ አመሻሹ ላይ እየመጣ ያነጋግራቸው ነበር፡፡ አዳምና ሔዋን እግዚአብሔር ከከለከላቸው ከአንድ ዛፍ በስተቀር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዲበሉ ተፈቅዶላቸው ነበር፡፡
የደብዳቤን ዋጋ የተረዳሁት ከአንድ አጎቴ በተላከልኝ፤ ነገር ግን በውስጡ ምንም ደብዳቤን ያልያዘ ፖስታ የደረሰኝ ዕለት ነው፡፡ ፖስታው ላይ አድራሻው በትክክል ተፅፎና ተገቢው ቴምብር ተለጥፎበት የነበረ ቢሆንም በፖስታው ውስጥ ግን ምንም አልነበረም፡፡ ብዙዎቻችን በተለያዩ ጊዜያት ከተለያዩ ቦታዎች ደብዳቤዎች ይደርሱናል፡፡ ነገር ግን ከደብዳቤ የምንማረው መንፈሳዊ ትምህርት በጣም ጥቂት ነው፡፡ ደብዳቤያችንን ወደ ፖስታ ቤት ይዘን ሄደን ወደ ምንፈልገው አድራሻ ከመላካችን በፊት ፖስታና ቴምብር (ወይም የመላኪያ ገንዘብ) ሊኖረን ይገባል፡፡ እነዚህን ነገሮች ካሟላን በኋላ የተጻፈውን ደብዳቤ በፖስታ ውስጥ በመጨመር ተገቢውን ቴምብር እንለጥፍበታለን፡፡ የፖስታ ቤት ሰራተኞች በፖስታችን ላይ የለጠፍነው ቴምብር በሌላ ሰው ግልጋሎት ላይ እንዳይውል ማህተም ይመቱበታል፡፡ በስተመጨረሻም ለመላክ የተዘጋጀውን ፖስታ በመላኪያ ሳጥን ውስጥ እንከተዋለን፡፡
“እነሆ፥ እውነትን ወደድህ፤ የማይታይ ስውር ጥበብን አስታወቅኸኝ” (መዝሙር 51፡6) ታማኝነት የእውነተኛ ህይወት መገለጫ ባህርይ ነው፡፡ ታማኝነት በዋናነት የልብ ጉዳይ ነው፡፡ ታማኝነት ከኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መሰረታዊ መመሪያዎች አንዱ ነው፡፡ እግዚአብሔር የልብን ሀሳብና መሻት ያውቃል፡፡ እውነተኝነት ለእግዚአብሔር መሰረታዊ መርህ ነው ምክንያቱም እርሱ የእውነት አምላክ ነው (ዘዳግም 32፡4)፡፡ ሙሉ በሙሉ ታማኝ የሆነ ልባችንን በእርግጥም ይባርካል፡፡ የሚታወቅብህ ከመሰለህ እውነትን፤ ማንም ማያውቅብህ ከሆነ ግን ውሸትን ትናገራለህን? ሆን ብለህ ሰዎችን ወደ ተሳሳተ አመለካከት ትመራቸዋለህ? መክፈል እንደማትችል እያወቅህ እዳ ውስጥ ትገባለህ? ስትፀልይ ያለህበትን ሁኔታ በግልጽ ለእግዚአብሔር ትናገራለህ? እግዚአብሔር እንድታደርግ ያሳወቀህን ሁሉ በታማኝነት ታደርጋለህ? ለመጽሀፍ ቅዱስ አትተምሮዎች ታማኝ ነህ? በሰዎች ፊት ሆነህ እንደምትቀርበው ዓይነት ሰው ነህን?
ህይወት እንደ ጉዞ መሆኑን ታውቅ ነበር? የህይወት ጉዞ ወደ ሁለት ቦታ የሚያደርሱ ሁለት ጎዳናዎች አሉት፡፡ በየትኛው መንገድ ላይ ለመጓዝ መምረጥና መወሰን የአንተ ነው፡፡ በአንድ ቤተሰብ ውስጥ ልጅ ሲወለድ የህይወትን ጉዞ ይጀምራል፡፡ በሰማይ የሚኖር አምላክ ለታዳጊ ልጆች ልዩ መንገድን ያደርጋል፡፡ ይሄ መንገድ የየዋህነት፣ እራስን ወደ ማወቅ የሚያመጣ መንገድ ነው፡፡ በዚህ መንገድ ላይ እናትና አባት ለልጆች ስለ ህይወት በማስተማር መሪዎች ናቸው፡፡
የሰው ልጅ ቅዱስ በሆነው በእግዚአብሔር ፊት በኃጢአቱ ወንጀለኛ ሆኖ በመገኘቱ ሞት እንደተፈረደበት ታውቃለህ? ከዚህ የዘላለም ሞት ፍርድ አምልጦ ለዘላለም ይድን ዘንድ የእግዚአብሔርን ምህረት መቀበል አለበት፡፡ ከዘላለም ሞት አንፃር ምህረት ማለት እግዚአብሔር የሰው ልጅ ሊቀበል ለሚገባው ፍርድ ይቅርታን ሲያደርግ ነው፡፡ ምንም እንኳ ድነት ነጻ የማይከፈልበትና በስራችን የምናገኘው ባይሆንም እግዚአብሔር ግን ምህረቱን ለሰው ልጅ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ አይደለም የሰጠው፡፡ እግዚአብሔር ምህረት የሚደርግበት ቅድመ ሁኔታ ንስሐ ነው፡፡
ጆን ሬይኖልድስ ከማውቃቸው ታሪኮች በጣም ያስደነቀኝና እና ያነቃኝ በጄፈርሰን ግዛት በፈረስ ስርቆት ታዋቂ የነበረው የጆርጅ ሊኖክስ ታሪክ ነው፡፡ ይህ ሰው ለሁለተኛ ጊዜ ተፈርዶበት በእስር ላይ ነበር፡፡ በመጀመሪያ የሴጅዊክ ግዛት በተመሳሳይ የፈረስ ስርቆት ወንጀል አስሮት ነበር፡፡
የዮሐንስ ወንጌል 10፡ 1-18 አንድ ሰው ሲጠራህና የሚጠራህ ሰው ድምጽ ከየት አቅጣጫ እንደሚመጣ ለማወቅ ግራ ተጋብተህ ታውቅ ይሆን? ወይም ብዙ ጫጫታ መካከል ከመሆንህ የተነሳ የሚጠራህን ሰው ድምጽ ለመስማት ተቸግረህ ታውቅ ይሆን? አድምጥ! አንድ ድምጽ እየጠራህ ነው፡፡ አዎ አንተን! አንተ ማን ነህ? ስምህ ማን ነው? ከየት ነው የመጣኸው? የት ነው ምትኖረው? ወዴትስ እየተጓዝክ ነው? የምትኖርበትን አካባቢ ስም ታውቃለህ፡፡ ድነገትም ከምትኖርበት አካባቢ ርቀህ ተጉዘህ አታውቅ ይሆናል፡፡ ነገር ግን የምትኖርበት አካባቢ የአንድ አገር አካል፤ አገራት ደግሞ የአለም አካል እንደሆኑ ታውቃለህ;፡፡
ሁሉም ሰው ይህንን “እድን ዘንድ ምን ማድረግ ይገባኛል?” የሚለውን ጠቃሚ ጥያቄ እራሱን ሊጠይቅ ይገባዋል፡፡ ብዙ ሰዎች ድነናል ብለው ቢያምኑም ኢየሱስ ግን ሲናገር “በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም” (ማቴዎስ 7፥21) ብልዋል፡፡ ድነትን ለማግኘት ክርስቶስ ኃጢአታችንን ይቅር እንደሚለን ማመን አስፈላጊ ነው፡፡ ከዛም ኃጢአታችንን መናዘዝ፣ በቅድስና መኖርና አንዳችን አንዳችንን በመውደድ በፍቅር ልንኖር ይገባል፡፡ በዚህ ዘመን የተለያዩ ኃይማኖቶች የተለያዩ ትምህርቶችን የሚያስተምሩ ሲሆን ሊጠየቅ የሚገባው መሰረታዊ ጥያቄ ግን “እውነት የትኛው ነው?” የሚለው ጥያቄ ነው፡፡
በአሁኑ ወቅት ሕያው ነዎት፤ ይተነፍሳሉ፤ ከቦታ ቦታ ይንቀሳቀሳሉ፤ ስራዎንም ያከናውናሉ፡፡ እየኖሩ ያሉት ሕይወት በምቾት ወይም በችግር የተሞላ ሕይወት ይሆናል፡፡ ፀሀይ ትወጣለች ደግሞም ትጠልቃለች፤ በአንድ ስፍራ ህጻን ይወለዳል በሌላ ስፍራ ደግሞ አንዱ ይሞታል፡፡ ሕይወት በአጠቃላይ ጊዜያዊ ቅንብር ነች፡፡ ነገር ግን እርስዎ ከሞቱ በኋላ ወዴት ይሄዳሉ? ኃይማኖተኛ ሰው ቢሆኑ፤ ወይም ምንም አይነት ኃይማኖት ባይኖርዎ ይህንን መሰረታዊ ጥያቄ መመለስ ይኖርብዎታል፡፡ ምክንያቱም ሰው ሁሉ ከአጭር የምድራዊ ቆይታው በኋላ ወደ ዘላለም መኖሪያው ያመራልና (መክብብ 12፡5)፡፡ ግን ወዴት? የሚቀበሩበት የመቃብር ስፍራ ነፍሶን ማስቀረት አይቻለውም፡፡ በድንዎ በእሳት ተቃጥሎ ቢጠፋ፤ ነፍስዎን እሳት አይበላትም፡፡ በጥልቁ ባህር ውስት ገብተው ቢጠፉ፤ ነፍስዎ አትሰምጥም፡፡ ነፍስዎ በፍጹም አትሞትም! የሰማይ እና የምድር ሁሉ አምላክ
ክፍሊቱ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ሙታንንም ታናናሾችንና ታላላቆችን በዙፋኑ ፊት ቆመው አየሁ፥ መጻሕፍትም ተከፈቱ፤ ሌላ መጽሐፍም ተከፈተ እርሱም የሕይወት መጽሐፍ ነው፤ ሙታንም በመጻሕፍት ተጽፎ እንደ ነበረ እንደ ሥራቸው መጠን ተከፈሉ” (ራእይ 20፥12) የሚል ጥቅስን እናነባለን፤ ይህም እግዚአብሔር የእያንዳንዳችንን ሕይወት መዝግቦ እንደሚያስቀምት ማስረጃ ነው፡፡
እኔ አንድ ወዳጅ አለኝ፡፡ እርሱ ከወዳጆቼ ሁሉ ይልቅ የቅርብ ወዳጄ ነው፡፡ እርሱ በጣም ደግና እውነተኛ ስለሆነ አንተም እንድትተዋወቀው እፈልጋለሁ፡፡ ስሙ ኢየሱስ ይባላል፡፡ እርሱ የአንተም ወዳጅ መሆን ስለሚፈልግ በጣም ድንቅ ነገር ነው፡፡ ስለ እርሱ ልንገርህ፡፡ የእርሱን ታሪክ ከመጽሐፍ ቅዱስ እናነባለን፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እውነትና የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ አለምና በአለም ውስጥ ያለውን ሁሉ የፈጠረ እግዚአብሔር ነው፡፡ እርሱ የሰማይና የምድር አምላክ ነው፡፡ እርሱ ሕይወትንና እስትንፋስን ለሁሉም ይሰጣል፡፡
ሰላም፤ ለአገራችን፣ ለቤታችን በተለይም ለልባችንና ለአእምሮአችን ሰላም የት ይገኛል? በሰዎች ዘንድ የሰላም የጥም ጩኸት ለዘመናት ሲያስተጋባ ኖርዋል፤ በተለይም ዓለም ከጊዜ ወደ ጊዜ እንደ አውሎ ንፋስ እየተናወጠችና ለአስደንጋጭ ክስተቶች ተጋላጭ እየሆነች በመጣች ቁጥር የሰላም ጉጉት ጩኸት ጎልቶ ይሰማል፡፡ ያንተስ የልብህ ጥማት ይሄ ነው? አለመርካትና ሁከት በነገሰበት ዓለም ውስጥ ሁሉን የሚያስንቅ ውስጣዊ ፀጥታን ማግኘት ትፈልጋለህ?
ሌባ ሳይታሰብ በሌሊት እንደሚመጣ ጌታም እንዲሁ በድንገት ይመጣል (2ኛ ጴጥሮስ 3፡19)፡፡ የጌታ የመምጫ ጊዜ ቅርብ እንደሆነ ለምን እናምናለን? በዙሪያህ እየሆነ ያለውን ስትመለከት፤ ምን ያሳስብሀል?